ዓለምአቀፋዊ ዜና

ሰሜን ኮሪያ ሊቃጣ የሚችልን ጥቃት በኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለመመከት ዝግጁ ነኝ አለች

By Feven Bishaw

July 29, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው ከየትኛውም አካል ሊቃጣ የሚችልን ጥቃት በኒውክሌር የጦር መሳሪያ አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል፡፡

ፒዮንግያንግ በፈረንጆቹ 1950 እስከ 1953 የተካሄደውን የሁለቱን ኮሪያዎች ጦርነት ያስቆመውን የጦር ሠራዊት 69ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በትናንትናው ዕለት አክብራለች፡፡