አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 3 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ሸዋ ዞን 7 ወረዳዎች በተካሔደ ድንገተኛ ፍተሻ ለተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ማስፈፀሚያ ሲውሉ የነበሩ 377 ሞተር ሳይክሎች መያዙን የዞኑ ፖሊስ አስታወቀ።
የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ኮማንደር አስቻለው ዓለሙ እንደገለጹት፥ የተያዙት ህገ ወጥ ሞተር ሳይክሎች የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው፣ ቦሎና የሶስተኛ ወገን የመድን ሽፋን ያልለጠፉ ናቸው ።