አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴው ግድብ ላይ ያላትን አቋም ለማስረዳት ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት ከፍተኛ የልኡካን ቡድኖችን በመላክ ላይ ትገኛለች።
በዚሁ መሰረት በኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ የተመራ ከፍተኛ የአገራችን የልኡካን ቡድን በዛሬው እለት ኬንያ ናይሮቢ በመገኘት ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ያላትን ግልጽ አቋም ለፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ አስረድቷል።