የሀገር ውስጥ ዜና

127 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

By Feven Bishaw

August 08, 2022

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 2 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ስምንት ቀናት 127 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዛቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ከሐምሌ 21 እስከ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ዘመቻ የኮንትሮባንድ እቃዎችን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 14 ሰዎችንም በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡