አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልሉ ብዝሃ ዋና ከተሞችና ሌሎች ተደራሽ በሆኑ ከተሞች ውስጥ ፍትሐዊ የልማት ስርጭትና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲኖር ተግተን እንሠራለን ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ፡፡
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ “የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት በክልሉ ሕዝቦች መካከል አብሮነትና አንድነትን በማጎልበት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እውን በማድረግ የጋራ ራዕይ የሆነውን ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል፡፡