የሀገር ውስጥ ዜና

በዳኝነት አካል ውስጥ የሙስና መከላከያ ስትራቴጂ መመሪያ ጸደቀ

By Feven Bishaw

August 15, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የፌደራል ፍርድ ቤቶች በዳኝነት አካል ውስጥ የሙስና ተግባራት መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ስትራቴጂ ማስፈጸሚያ መመሪያን አጸደቀ፡፡

ጉባኤው ዛሬ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ነው የፌደራል ፍርድ ቤቶች በዳኝነት አካል ውስጥ የሙስና ተግባራት መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ስትራቴጂ ማስፈጸሚያ መመሪያን ያጸደቀው፡፡