አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)ትንናት ምሽት ወደ አዲስ አበባ ሊገቡ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች መያዛቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
የጦር መሳሪያዎቹ የተያዙት መነሻውን ኮንሶ ባደረገ ላንድ ክሩዘር ተሽከርካሪ 16 ክላንሽኮቭ ፣ ዘጠኝ ምንሽር እና 14 ባዶ ካዝና በተሽከርካሪዉ አካል ላይ በተሰራ ድብቅ አካል (ሻግ) ዉስጥ ተደብቆ ወደ አዲስ አበባ ሊገባ ሲል በቱሉ ዲምቱ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ነው፡፡