አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን ከጫካ ወደ ማዕከል ለተመለሱ ዜጎች የተጠናከረ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ድጋፍ ሰጪ ግብረ ሃይሉ ገለፀ፡፡
በዞኑ በዳንጉር ወረዳ እየተካሄደ ያለውን ህግ የማስከበር ተግባር ተከትሎ ከሰባት ቀበሌዎች ተፈናቅለው በጸረ ሰላም ሃይሎች ተጽዕኖ ጫካ ውስጥ የነበሩ ከ10 ሺህ 200 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተመልሰው በአይሲካ ማዕከል ተጠልለው ይገኛሉ።