አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዜግነት አገልግሎት ነፃ የጤና ምርመራ እና የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስራ ‘’በጎነት ለጤናችን’’ በሚል መሪ ቃል በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል መሰጠት ተጀመረ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተርዮሐንስ ጫላ እንደገለጹት÷ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ ዕድሜአቸው ከ50 ዓመት በላይ ለሆኑ አቅመ ደካሞች ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነፃ የህክምና አገልግሎት ይሰጣል፡፡
መርሐ ግብሩን ያስጀመሩት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ÷ በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ የተለያዩ የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የተጀመረው መርሐ ግብርም መክፈል የማይችሉ ዜጎች በነፃ የህክምናና የምርመራ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በቀጣይ መሰል የበጎ ፈቃድ ተግባራት በሌሎች ዘርፎች ላይ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ነው የገለጹት፡፡
የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ያሲን አብዱላሂ በበኩላቸው÷ ነፃ የምርመራና የህክምና አገልግሎቱ አቅመ ደካማ የሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎችን እና ኑሯቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ 5 ሺህ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡