አዲስ አበባ፣ ነሐሴ16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2014 በጀት ዓመት ሀገር ልታጣ የነበረውን 50 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ማዳን መቻሉን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ የገቢዎች ሚኒስሯ ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ እና የኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የ2014 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ላይ እየተወያየ ነው፡፡