የሀገር ውስጥ ዜና

የበጎ ፍቃድ አገልገሎትን አንድነትን ለማጠናከር መጠቀም እንደሚገባ ተገለፀ

By Feven Bishaw

August 22, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የክረምት በጎ ፍቃድ አገልገሎትን ኢትዮጵያዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚያስችል መልኩ መጠቀም እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ የትምህርት ፣ ባህልና ቱሪዝም ፣ ፋይናንስ ፣ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢዎች እና የሌሎችን ተቋማት የክረምት በጎ ፍቃድ አተገባበር ተመልክተዋል፡፡