የሀገር ውስጥ ዜና

የሲቪል ማህበራትና የፖለቲካ ፓርቲ ምክር ቤቶች በሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ላይ እየመከሩ ነው

By Feven Bishaw

August 23, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ላይ የበኩላቸውን መወጣት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ እየመከሩ ነው።

በውይይቱ ላይ ሁለቱ ምክር ቤቶች በሀገራዊ ጥቅም ላይ በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸው ተገልጿል።