የሀገር ውስጥ ዜና

የሠራዊቱን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ባልተረጋገጡ መረጃዎችና አሉባልታዎች የማራገብ ሙከራዎች እንዲቆሙ ሚኒስቴሩ አሳሰበ

By Feven Bishaw

August 23, 2022

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሠራዊቱን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ባልተረጋገጡ፣ ባልተገቡ መረጃዎችና አሉባልታዎች የመዘገብ ወይም የማራገብ አሉታዊ ሙከራዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ የመከላከያ ሚኒስቴር አሳሳበ።

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ የህዝቡ ድጋፍ እና ተሳትፎ ጠንካራ መሆን፤ መከላከያ ሰራዊት የሀገር ሉዓላዊነትን ለመጠበቅ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት ወሳኝ መሆኑን በፅናት ያምናል ብሏል፡፡