የሀገር ውስጥ ዜና

የሶለል በዓል በቆቦ ከተማ በድምቀት ተከበረ

By ዮሐንስ ደርበው

August 23, 2022

 

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶለል በዓል “ሶለልን በግንባር ለድልና ለነፃነት” በሚል መሪ መልዕክት በቆቦ ከተማ በድምቀት ተከብሯል፡፡

የቆቦ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሰይድ አባተ በበዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ የሶለል በዓል በአሸባሪው ህወሓት ወረራ ምክንያት ባለፈው ዓመት ሳይከበር መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡