የሀገር ውስጥ ዜና

ኢኮኖሚን ከውጭ ሀገራት ጥገኝነት ለማላቀቅ ቀጣይ ሊተኮርባቸው የሚገቡ ስራዎች እንዳሉ ተመላከተ

By Feven Bishaw

August 24, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከውጭ ሀገራት ጥገኝነት ለማላቀቅ መንግስት እየሰራው ያለው ስራ መልካም ቢሆንም ቀጣይ ሊተኮርባቸው የሚገቡ ስራዎች እንዳሉ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ተናግረዋል።

ግብርናውን ወደ ሰፋፊ ሜከናይዜሽን መቀየር፣ ኢንዱስትሪውን ማሳደግ እና የተሻለ ውጤት ሊገኝባቸው የሚችሉ ዘርፎች ላይ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ በመስራት ማሻሻል እንደሚገባ ምሁራኑ ይገልጻሉ።