አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከውጭ ሀገራት ጥገኝነት ለማላቀቅ መንግስት እየሰራው ያለው ስራ መልካም ቢሆንም ቀጣይ ሊተኮርባቸው የሚገቡ ስራዎች እንዳሉ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ተናግረዋል።
ግብርናውን ወደ ሰፋፊ ሜከናይዜሽን መቀየር፣ ኢንዱስትሪውን ማሳደግ እና የተሻለ ውጤት ሊገኝባቸው የሚችሉ ዘርፎች ላይ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ በመስራት ማሻሻል እንደሚገባ ምሁራኑ ይገልጻሉ።