የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ የአበዳሪ ሀገራት ኮሚቴ የብድር ሽግሽግን በተመለከተ ላሳለፈው ውሳኔ አድናቆቷን ገለፀች

By Feven Bishaw

August 24, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት የአበዳሪ ሀገራት ኮሚቴ የሀገሪቱን የብድር ሽግሽግን በተመለከተ ያሳለፈውን ውሳኔ በበጎ ጎን እንደሚቀበለው የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ የአበዳሪዎች ሀገራት ኮሚቴ ኢትዮጵያ የእዳ ጫናን ለማቅለል ያቀረበችውን የብድር ሽግሽግ በተመለከተ ምክክር ማድረጉን አስታውቋል፡፡