የሀገር ውስጥ ዜና

የብሪታንያው “ዩኒሊቨር” ኩባንያ በኢትዮጵያ በምግብ ማቀነባበር ዘርፍ መሰማራት እንደሚፈልግ ገለጸ

By ዮሐንስ ደርበው

August 25, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በለንደን የሚገኘው “ዩኒሊቨር” የተባለው ኩባንያ በኢትዮጵያ የምግብ ማቀነባበር ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ፡፡

በእንግሊዝ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ተፈሪ መለሰ ከዩኒሊቨር ኩባንያ የአፍሪካ ኮርፖሬት ጉዳዮች ዳይሬክተር ዳጊ በሩ ጋር ተወያይተዋል፡፡