የሀገር ውስጥ ዜና

በ17ኛው የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አስተዳደር ዝግጅት ሂደት ላይ ምክክር ተካሄደ

By ዮሐንስ ደርበው

August 25, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 17ኛው የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አስተዳደር ዝግጅት ሂደትን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ÷ ኢትዮጵያ 17ኛውን የኢንተርኔት አስተዳደር ጉባኤ በ2022 እንድታስተናግድ መመረጧን አስታውሰዋል፡፡