አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ሀሰተኛ ሰነዶችንና ማስረጃዎችን ሲያዘጋጁ የነበሩ 13 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት ግለሰቦች መካከል ሰባቱ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት የወሳኝ ኩነት ሰራተኞች ሲሆኑ÷ ስድስቱ ደግሞ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ በመኖሪያ ቤታቸው ሕገወጥ ማስረጃዎቹን ሲያዘጋጁ በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ናቸው፡፡