የሀገር ውስጥ ዜና

መንግስት በትግራይ የሚኖሩ ዜጎች ከጁንታው ወታደራዊ መሣሪያዎችና ማሠልጠኛዎች እንዲርቁ መልዕክት ማስተላለፉ ለዜጎች የሚሰማውን ኃላፊነት እንደሚያሳይ ተገለጸ

By Feven Bishaw

August 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግሥት በትግራይ የሚኖሩ ዜጎች ከሽብርተኛው ህወሓት ወታደራዊ መሣሪያዎችና ማሠልጠኛዎች እንዲርቁ መልዕክት ማስተላለፉ ለዜጎች የሚሰማውን ኃላፊነት የሚያሳይ መሆኑን የቀድሞ ሠራዊት አባል የሆኑት ብርጋዴር ጄነራል ካሳዬ ጨመዳ ገለጹ፡፡

ብርጋዴር ጄነራል ካሳዬ ጨመዳ እንደተናገሩት÷ አሸባሪው ህወሓት ሰሞኑን እያወጣቸው የነበሩ መግለጫዎችና ሲያሰራጫቸው የነበሩ የሐሰት መረጃዎች ቡድኑ ለጦርነት ሲዘጋጅ እንደቆየ በግልጽ የሚያሳዩ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡