አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን “ሀገራችን ሰላም እንድትሆን ጦርነት እስኪያበቃና የሀገር ሉዓላዊነት እስከሚከበር ከመንግስት ጋር በመሆን የበኩላችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን” ሲሉ አረጋገጡ፡፡
በኬንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የአሸባሪው ሕወሃት ቡድንን በማውገዝ ባለ 6 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።