የሀገር ውስጥ ዜና

ዶክተር ሙላቱ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያን አቋም የሚያስረዳ መልዕክት ለአውሮፓ ህብረት መሪዎች እና ለፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት አደረሱ

By Tibebu Kebede

March 16, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያን ግልጽ አቋም የሚያስረዳ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተላከ መልዕክት ለአውሮፓ ህብረት መሪዎች እና ለፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት አደረሱ።

የቀድሞው ፕሬዚዳንት ለአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ቻርለስ ሚካኤል የተላከውን መልዕክት ለካቢኔ ሃላፊው ፍራንኮስ ሩክስ እና ለአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮንደር ለይን የተላከውን መልዕክት ለአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ቦሬል አድርሰዋል።