አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በቤት ልማት ፋይናንስ አቅርቦት ዙሪያ ከከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችና የፋይናንስ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡
ውይይቱ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እዮብ ተካልኝን ጨምሮ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንትና የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡