አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐሰተኛ መረጃና በአሉባልታ የተወሰነ አለመረጋጋት ታይቶባት የነበረችው ወልዲያ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴዋ መመለሷ ተገለጸ፡፡
ወልዲያ ከተማ ከሰሞኑ በወራሪው ህወሓት ስምሪት ተሰጥቷቸው ወደከተማዋ የገቡ ሰርጎ ገቦች ከተማዋ በአሸባሪው ቡድን ልትያዝ መሆኑን በነዙት የማደናገሪያ አሉባልታ ጥቂት የከተማዋ ነዋሪዎች ከተማዋን ለቀው ወደ አጎራባች አካባቢዎች መሄዳቸው ይታወሳል፡፡