አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ከበዓል ጋር ተያይዞ የዋጋ ንረት እንዳይፈጠር የተመረጡ የምግብ ፍጆታዎች ለህብረተሰቡ እየቀረቡ መሆኑን የከተማዋ ንግድ ቢሮ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ አደም ኑሪ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ከመጪው የዘመን መለወጫ እና ሌሎች በዓላት ጋር ተያይዞ በምግብ ፍጆታ ሸቀጦች ላይ የአቅርቦት እጥረት እና የዋጋ ንረት እንዳይከሰት በልዩ ትኩረት እየተሠራ ነው፡፡