የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ 100 ሺህ ሔክታር በሩዝ ምርት ተሸፍኗል

By Feven Bishaw

September 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በክረምት እርሻ 100 ሺህ ሔክታር በሩዝ ምርት መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ምክትል ኃላፊ ጌቱ ገመቹ ለፋና ብሮድካስንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በዘንድሮው የክረምት እርሻ 6 ነጥብ 3 ሚሊየን ሔክታር በተለያየ ሰብል ተሸፍኗል፡፡