የሀገር ውስጥ ዜና

ከተማ አስተዳደሩ በቂርቆስ ክ/ ከተማ የተገነቡ ቤቶችን ለአቅመ ደካማ ወገኖች አስረከበ

By Feven Bishaw

September 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ጵጉሜን 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የተገነቡ ቤቶችን ለአቅመ ደካማ ወገኖች አስረክቧል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በክፍለ ከተማው ወረዳ 3 በመከላከያ ኮንስትራክሽን አማካኝነትና በሄይንከን ኢትዮጵያ የተገነቡ ቤቶችን መርቀው ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቁልፍ አስረክበዋል፡፡