የሀገር ውስጥ ዜና

ዶክተር በለጠ ሞላ ከቶኒ ብሌር ጋር ተወያዩ

By ዮሐንስ ደርበው

September 07, 2022

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ ከቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት መስራች፣ ሊቀመንበር እና የቀድሞው የታላቋ ብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቶኒ ብሌር ጋር በትብብር ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

ዶክተር በለጠ ኢንስቲትዩቱ በተለይም በዲጂታል መንግሥት፣ በዲጂታል ግብይትና መታወቂያ፣ በዲጂታል መሰረተ ልማትና መሰል ሥራዎች ላይ እያደረገ ያለውን ድጋፍ ማድነቃቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡