የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ ከኮሮናቫይረስ ነጻ መሆናቸው ታወቀ

By Tibebu Kebede

March 17, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮናቫይረስ ከተያዘው ጃፓናዊ ጋር ንክኪ የነበራቸው የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው ተገለጸ።

ከ12 ቀናት በፊት ከጃፓናዊው ጋር ንኪኪ የነበራቸው  21 ሰዎች ነጻ መሆናቸውን በሐኪሞች እንደተገለጸላቸው ዶክተር ቶላ ተናግረዋል።