አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በያዝነው ዓመት ስምንት የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡
የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ክብሮም ካህሳይ እንደገለጹት÷ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት በውጪ ሥራ ተቋራጮችና በተቋሙ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ ይከናወናል፡፡