የሀገር ውስጥ ዜና

በአሸባሪው ህወሓት ለተጎዱ ዜጎችና ተቋማት 5 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ ድጋፍ ተደረገ

By ዮሐንስ ደርበው

September 14, 2022

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 4 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው ህወሓት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎችና የጤና ተቋማት 5 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን የኢትዮ-ካናዳውያን ኔትወርክ ለማህበራዊ ድጋፍ አስታውቋል፡፡

ድጋፉ በአማራና አፋር ክልሎች በጦርነት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖችና የጤና ተቋማት ተደራሽ መደረጉ ተገልጿል፡፡