የሀገር ውስጥ ዜና

12ኛው የጣና ፎረም ጉባዔ በጥቅምት ወር ይካሄዳል

By ዮሐንስ ደርበው

September 16, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጣና ፎረም በመጪው ጥቅምት ወር አጋማሽ በባሕርዳር ከተማ እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡

የ2015 ዓ.ም ጣና ፎረም ጉባዔ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አስመልክቶ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ ከጣና ፎረም አዘጋጅ ኮሚቴ ጋር ተወያይተዋል።