ዓለምአቀፋዊ ዜና

የኒውክሌር ስምምነት ላይ ለመድረስ ማዕቀቦች መነሳት አለባቸው- ኢራን

By ዮሐንስ ደርበው

September 16, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ የኒውክሌር ስምምነት ላይ ለመድረስ አሜሪካ የጣለቻቸውን ማዕቀቦች ማንሳት እንዳለባት ገለጹ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መርሐ ግብሯ በዘላቂነት ለማስወገድ ከአሜሪካ በኩል አስተማማኝ ዋስትና ልታገኝ ይገባል ብለዋል።