አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች ተጠናክሮ እንዲቀጥል በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ የደቡብ አፍሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሙክታር ከድር ከደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ኬሲ ማሼጎ ድላሚኒ ጋር በሁለትዮሽ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡