የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ ክልል ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 200 ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

By Tibebu Kebede

March 18, 2020

አዲስ አበባ መጋቢት 9፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ ከ200 በላይ የንግድ ተቋማት መታሸጋቸውን የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ የተለያዩ ሁኔታዎችን በመጠበቅ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ የንግድ ተቋማት ላይ የንግድ ፍቃድ የመቀማትና ለህግ የማቅረብ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቢሮው ሃላፊ አቶ ዴንጌ ቦሩ ተናግረዋል።