አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በመሬት መንሸራተት ምክንያት ተዘግቶ የነበረው ጋምቤላን ከአዲስ አበባ የሚያገናኘው የአስፓልት መንገድ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጅማ ዲስትሪክት አስታወቀ።
የዲስትሪክቱ የራስ ኃይል የመንገድ ጥገና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር መሰረት ደጀኔ እንዳሉት÷ የአስፓልት መንገዱ “ኩላሊቴ ተራራ” ተብሎ የሚጠራ አካባቢ ከጳጉሜን 4 ቀን ጀምሮ በአካባቢው የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሸራተት ምክንያት ተዘግቶ ቆይቷል ።