የሀገር ውስጥ ዜና

የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር ተገናኘ

By ዮሐንስ ደርበው

September 19, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር የማገናኘት ሥራ በስኬት መከናወኑ ተገለጸ፡፡

የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጁ ሙሉቀን ተሰማ እንደተናገሩት ÷ 40 ሜጋ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጩ 16 የንፋስ ተርባይኖች የፍተሻና ሙከራ ሥራ ተጠናቆ ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ጋር የማገናኘት ሥራ ተሰርቷል፡፡