የሀገር ውስጥ ዜና

የደብረ ብርሀን ከተማ ምክትል ከንቲባን ጨምሮ አምስት ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

By Tibebu Kebede

March 18, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የደብረ ብርሀን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ደስታ አንዳርጌን ጨምሮ አምስት ባለሙያዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የከተማው ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ኮማንደር ታዬ ወልደጊዮርጊስ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከከተማ መሬት ጋር በተያያዘ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው።