የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ አማኑኤል አካባቢው በጎርፍ አደጋ የወደሙ ቤቶች ግንባታ ተጀመረ

By Feven Bishaw

September 21, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አማኑኤል አካባቢ በተፈጥሮ አደጋ የመኖሪያ ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች ዛሬ የመልሦ ግንባታ ሥራ ተጀምሯል፡፡

የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር ዓባይ በመልሦ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ እንዳሉት÷ ከተማ አስተዳደሩ ሰው ተኮር ሥራዎችን እየሠራ ነው፡፡