የሀገር ውስጥ ዜና

የሙያተኝነት መስፈርትን ሳያሟላ የተዘጋጀውን የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ሪፖርት የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባላት እንዲቃወሙ ኢትዮጵያ ጠየቀች

By ዮሐንስ ደርበው

September 21, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ያቀረበውን ከደረጃ በታች የወረደ ሪፖርት የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባላት እንዲቃወሙ ኢትዮጵያ ጥሪ አቀረበች።

በጄኔቫ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ፅህፈት ቤት በጉዳዩ ላይ ባወጣው መግለጫ፥ የተመድ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሰሜኑን ግጭት ተከትሎ ሊኖሩ የሚችሉ የመብት ጥሰቶችን በጋራ ምርመራ በማድረግ ሪፖርት ማውጣታቸውን አስታውሷል።