አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተስተዋለ ያለውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቆራረጥ ችግር ለመቅረፍ ያለመ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ ላይ የቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሽፈራው ተሊላ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክፍሌ ሆሮ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ካሣሁን ከበደን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡