የሀገር ውስጥ ዜና

ለመከላከያ ሠራዊት ከ5 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ ተደረገ

By ዮሐንስ ደርበው

September 21, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ዞኖች ለመከላከያ ሠራዊት ከ5 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው የአይነት ድጋፍ አደረጉ፡፡

የአዊ ብሔረሰብ አስተዳዳር ዞን ያሰባሰበውን ከ5 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ በሰቆጣ ከተማ ለሠራዊቱ አስረክቧል፡፡