አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ችግር እንዳይገጥማቸው በሀገሪቱ መሪዎች ጭምር ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ ተባብሮና ተመካክሮ ችግሮችን ለመቅረፍ ዝግጁ መሆናቸውን የሱዳን የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡
በሱዳን የኢፌዴሪ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ከሱዳን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሌተናል ጄኔራል አናን ሃሚድ ሞሃመድ ኦማር እና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስር ያሉ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡