የሀገር ውስጥ ዜና

የህግ የበላይነትንና የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ስርዓቱን የማስጠበቅ መደበኛ ስራ ይቀጥል- ጠቅላይ አቃቤ ህግ

By Tibebu Kebede

March 19, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ የህግ የበላይነትንና የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ስርዓቱን የማስጠበቅ መደበኛ ስራ እንደሚቀጥል ገለፀ።

የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ቱኑ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በተመለከተ እና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።