አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ማዲንጎ የተዋጣለት ከያኒ ብቻ ሳይሆን ልበቀናና ሀገር ወዳድ ነበር ሲሉ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ሕልፈተ ሕይወት እጅግ አሳዛኝ ክስተት ነው ብለዋል፡፡
ማዲንጎ የተዋጣለት ከያኒ ብቻ ሳይሆን÷ ልበቀናና ሀገር ወዳድ፣ እንደሰው ሰከን ያለ ሰብዕና የተላበሰ ሰው እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ባደረበት ህመም ምክንያት ዛሬ ሕይወቱ ማለፉ ይታወሳል፡፡