አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማኅበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ተሳታፊ ሀገራት አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል።
ከተሳታፊ ሀገራት መካከል የብሩንዲ፣ የደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ከ17 ዓመት ብሔራዊ ቡድኖች ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ መግባታቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።