አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መስከረም 21 ቀን 2015 ዓ.ም የሚከበረው የግሸን ደብረ ከርቤ ዓመታዊ የንግሥ በዓል ያለምንም የጸጥታ ችግር ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የደቡብ ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር እርገጤ ጌታሁን ባለፉት ዓመታት በኮሮና ወረርሽኝ እና የሽብር ቡድኑ ህወሓት በከፈተው ጦርነቱ ምክንያት ብዙ ምዕመናን መምጣት አለመቻላቸውን አስታውሰዋል፡፡