የሀገር ውስጥ ዜና

የኮምቦልቻ ከተማ ነዋሪዎች ለመከላከያ ሠራዊት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ አደረጉ

By ዮሐንስ ደርበው

September 28, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች በግንባር ለሚገኘው መከላከያ ሠራዊት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ድጋፉ የእርድ ሰንጋ፣ ለስላሳ መጠጦችንና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁስ ያካተተ ነው፡፡