አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አገራዊ የምክክር ሂደቱን በገንዘብ ለመደገፍ የሚያስችል የፕሮግራም ሰነድ ስምምነት በገንዘብ ሚኒስቴር፣ በአገራዊ የምክክር ኮሚሽንና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም መካከል ተፈረመ፡፡
ለሦስት ዓመታት ተግባራዊ በሚደረገው በዚህ የፕሮግራም ሰነድ፥ የመንግስታቱ ድርጅት የልማት ፕሮግራም ከልማት አጋሮች ፈንድ ለማሰባሰብ የፋይናንስ ቋት በመክፈት የሚያስተዳድር መሆኑ ተገልጿል፡፡