የሀገር ውስጥ ዜና

በ13ኛው ዙር እጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች የውል ስምምነት የወሰን ውዝግብ ያለባቸውን እንደማያካትት ተገለፀ

By Tibebu Kebede

March 19, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ13ኛው ዙር እጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እየተከናወነ ያለው የውል ስምምነት የወሰን ውዝግብ ያለባቸውን ቤቶች እንደማያካትት ተገለፀ።

ሰሞኑን በተለያየ የግል ምክንያት እጣ ወጥቶላቸው ውል ያልተፈራረሙ እድለኞችን ውል የማፈራረም ስራ እተከናወነ ይገኛል።